ይህንን ቃል የተናገረው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው፡፡ አንድ አንድ ጊዜ ይህንን ቃል በምናነብበት እና በምንሰማበት ጊዜ እንዴት ዐይን እያላቸው ማየት አይችሉም? የሚል ጥያቄ በውስጣችን ሊነሳ ይችላል፡፡ ነገር ግን ገባ ብለን ወስጡን ስንመለከተው “ዐይን እያላቸው ማየት የማይችሉ” ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ በወቅቱ የነበረው ነቢይ ለጊዜው የተናገረው በተለያየ መልኩ ተሰርተው በሰዎች ዘንድ ይመለኩ የነበሩ ጣዖታትን ለመግለጽ ፈልጎ ነው፡፡ ቃሉ ግን በተለያየ ጊዜ የተነሱ ሰዎችን ማለትም ሁሉን መርምሮ ማወቅ የሚችል ኅሊና ተሰጥቷቸው ብርሃኑን ከጨለማ፣ እውነቱን ከሃሰት፣ ጥሩውን ከመጥፎው ለይተው እራሳቸውን አና የሚከተላቸውን ሰው በመጥቀም ፈንታ ሰውን የሚጎዱ እና በተሳሳተ መንገድ የሚመሩ ብዙ ሰዎችን ይገልጻል፡፡እንደዚህ አይነት ሰዎች በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በተለያዩ ዘመናት ተነስተዋል አሁንም አሉ ወደፊትም ይቀጥላሉ፡፡ከነዚህም ውስጥ በዘመነ ነቢያት የነበሩት እግዚአብሔር በነቢያቱ አድሮ የሚያስተላልፈውን ትምህርት አና ተግሳጽ ወደ ጎን በመተው እና በራሳቸው መንገድ በመሄድ ፍጻሜያቸው ስቃይ እና ሞት የሆነባቸው ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ከዚህ ዘመን በኋላ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም በመጣበት ጊዜ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚያሰተምረውን ትምህርት እየሰሙ፣ የእጁን ታምራት እያዩ በአጠቃላይ የሚያደርገውን ድንቅ የሆነ ነገር እያዩ እንዳላዩ ሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሁልጊዜ ይቃወሙት ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይቃወሙት የነበረ ጥፋት ኖሮበት ሳይሆን እነሱ የነበራቸውን ስጋዊ አላማ፣ወስጣዊ ፍላጎት፣ ዝርፊያ እንዲሁም እራሳቸውን ጻድቅ፣ እውነተኛ እና ለስራዓቱ ተቆርቋሪ በመምሰል በውስጣቸው ግን መራራ፣ ድብቅ የሆነና ከእውነት የራቀ ህዝቡን የማደናገር ሴራ ስለነበራቸው ይህንን ጉዳያቸውን ያደነቅፍብናል ብለው ስለሚያስቡ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ውስጡ ጥበበ እግዚአብሔር ቢኖርበትም ጌታችንን ለመስቀል በቅተዋል፡፡ የሚገርመው ነገር ግን ያሰቡት ነገር ሳይሳካላቸው መቅረቱ ነው፡፡ ምክናያቱም ከእርሱ የተማሩት ሐዋርያት በአምላካቸው መሪነት ጨው በመሆን ከጽንፍ እሰከ ጽንፍ ወንጌልን በማስተማር አልጫ የነበረውን ዓለም አጣፍጠዋል፡፡ ዐይን እያላቸው የማያዩ ሰዎች በሰማዕታት ዘመንም ተነስተው ብዙ ቅዱሳን አባቶቻችንን በልዩ ልዩ ስጋዊ መከራ በማሰቃየት ለሰማዕትነት አብቀተዋቸዋል፡፡ ሰማዕታትም የሚመጣባቸውን መከራ በመታገስ እና ሁሉን ቻይ የሆነውን የአምላካቸውን ስም በመጥራት እና እስከሞት ድረስ በመታመን የድል አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡ ከሐዋርያት የተረከቧትን እወነተኛዋን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትንም ከእነሱ በኋላ ላለው ትውልድ አስተላልፈዋል፡፡ከእነሱ በኋላ የተነሱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንም ሳትበረዝ እና ሳትከለስ አሁን ላለው ትውልድ አስተላልፈዋታል፡፡ የሚገርመው ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት የተነሱ ሆድ አደሮች፤ አይነ ስጋቸው ብቻ የተከፈተላቸው አይነ ልቡናቸው ግን የታወረባቸው፤ ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ ከገለጻቸው ጣዖታት የማይሻሉ ማለትም ሕይዎት ያላቸው ተንቀሳቃሽ ጣዖታት የሚያሰሙት የትታደስ ጩኸት ነው፡፡ በጣም የሚገርም እና የሚደንቅ ነገር ነው፡፡ በእውኑ እነዚህ ሰዎች የእምነት አርበኛ ከነበሩት፣ ሌሊት ከቀን ለጸሎት እና ለስግደት ይተጉ ከነበሩት፣ ሀይማኖታችንን አናስለውጥም፣አንክድም ብለው እሰከመጨረሻው ድረስ በመታገስ መራራ ሞትን ከቀመሱት ቅዱሳን አባቶቻችን ይበልጣሉን? ይህንን ጥያቄ ሁላችን በህሊናችን ልንጠይቅ ያስፈልጋል፡፡ የቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ሆይ እነዚህ ሰዎች እራሳቸው ጠፍተው ሰውን ለማጥፋት የተነሱ የዲያብሎስ መልእክተኞች ናቸውና ማንነታቸውን በመረዳት ከቤታችን ልናስወጣቸው ያስፈልጋል፡፡ በምን እናውቃቸዋለን ብንል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መመሪያ ሰጥቶናል ይኸውም “ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ” የሚል ነው፡፡ ማንም ሰው ጌታችን በደሙ ከመሰረታት እና ለሐዋርያት ከሰጣት ከአንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት እና ስርዓት ውጭ እንግዳ ትምህርት እና የእምነት ዶግማ እንዲሁም ቀኖና እና ስርዓት የሚያመጣ ሁሉ እርሱ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ወገን አይደለም፡፡እነዚህ ሰዎች ምንም ሳይማሩ ታሪክ አዋቂ በመምሰል እና አዲሱን ትውልድ ለማወናበድ እንዲሁም በግብጽ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የአባይ ጉዳይ እንደ ክፍተት በመጠቀም አሁን በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ያለውን አውነተኛ ዶግማ እና ስርዓት የግብጽ ሰዎች ኢትዮጵያን ለመበቀል እና ኋላቀር ለማድረግ ያመጡት ስርዓት ነው በማለት የትታደስ ጩኸት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ እውነታው ግን እነሱ እንደሚሉት አይደለም፡፡ ስለዚህ ክፍተት የሚመስሉ ነገሮችን እንደ መነሻ ሀሳብ በማንሳት እውነታውን ግን ጥላሸት በመቀባት በአባቶቻችን ዘመን ታይቶ የማይታወቅ አስተምህሮ ቀስ በቀስ ወደቤተክርስቲያን ውስጥ በማስገባት፤ እያወቁም ይሁን ሣያውቁ የሚከተሏቸውን የውኃንን ለዲያብሎስ እራት ለማድረግ የሚተጉ፣ ዐይን እያላቸው የማያዩ እና የማያስተውሉ ተሃድሶወችን ይህንን ስውር ሴራ እንደያዙ አውቀን ልንቃወማቸው ያስፈልጋል፡፡ አምላክ ቅዱሳን ቤተክርስትያናችንን ከውጭ ወራሪ ከውስጥ ጠላት ይጠብቅልን እኛንም በቤቱ ያጽናን አሜን!!!
Thursday, April 14, 2016
“ዐይን ቦሙ ወኢይሬእዩ” “ዐይን አላቸው አያዩም” መዝ 113፡13
ይህንን ቃል የተናገረው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው፡፡ አንድ አንድ ጊዜ ይህንን ቃል በምናነብበት እና በምንሰማበት ጊዜ እንዴት ዐይን እያላቸው ማየት አይችሉም? የሚል ጥያቄ በውስጣችን ሊነሳ ይችላል፡፡ ነገር ግን ገባ ብለን ወስጡን ስንመለከተው “ዐይን እያላቸው ማየት የማይችሉ” ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ በወቅቱ የነበረው ነቢይ ለጊዜው የተናገረው በተለያየ መልኩ ተሰርተው በሰዎች ዘንድ ይመለኩ የነበሩ ጣዖታትን ለመግለጽ ፈልጎ ነው፡፡ ቃሉ ግን በተለያየ ጊዜ የተነሱ ሰዎችን ማለትም ሁሉን መርምሮ ማወቅ የሚችል ኅሊና ተሰጥቷቸው ብርሃኑን ከጨለማ፣ እውነቱን ከሃሰት፣ ጥሩውን ከመጥፎው ለይተው እራሳቸውን አና የሚከተላቸውን ሰው በመጥቀም ፈንታ ሰውን የሚጎዱ እና በተሳሳተ መንገድ የሚመሩ ብዙ ሰዎችን ይገልጻል፡፡እንደዚህ አይነት ሰዎች በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በተለያዩ ዘመናት ተነስተዋል አሁንም አሉ ወደፊትም ይቀጥላሉ፡፡ከነዚህም ውስጥ በዘመነ ነቢያት የነበሩት እግዚአብሔር በነቢያቱ አድሮ የሚያስተላልፈውን ትምህርት አና ተግሳጽ ወደ ጎን በመተው እና በራሳቸው መንገድ በመሄድ ፍጻሜያቸው ስቃይ እና ሞት የሆነባቸው ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡ከዚህ ዘመን በኋላ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም በመጣበት ጊዜ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚያሰተምረውን ትምህርት እየሰሙ፣ የእጁን ታምራት እያዩ በአጠቃላይ የሚያደርገውን ድንቅ የሆነ ነገር እያዩ እንዳላዩ ሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሁልጊዜ ይቃወሙት ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይቃወሙት የነበረ ጥፋት ኖሮበት ሳይሆን እነሱ የነበራቸውን ስጋዊ አላማ፣ወስጣዊ ፍላጎት፣ ዝርፊያ እንዲሁም እራሳቸውን ጻድቅ፣ እውነተኛ እና ለስራዓቱ ተቆርቋሪ በመምሰል በውስጣቸው ግን መራራ፣ ድብቅ የሆነና ከእውነት የራቀ ህዝቡን የማደናገር ሴራ ስለነበራቸው ይህንን ጉዳያቸውን ያደነቅፍብናል ብለው ስለሚያስቡ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ውስጡ ጥበበ እግዚአብሔር ቢኖርበትም ጌታችንን ለመስቀል በቅተዋል፡፡ የሚገርመው ነገር ግን ያሰቡት ነገር ሳይሳካላቸው መቅረቱ ነው፡፡ ምክናያቱም ከእርሱ የተማሩት ሐዋርያት በአምላካቸው መሪነት ጨው በመሆን ከጽንፍ እሰከ ጽንፍ ወንጌልን በማስተማር አልጫ የነበረውን ዓለም አጣፍጠዋል፡፡ ዐይን እያላቸው የማያዩ ሰዎች በሰማዕታት ዘመንም ተነስተው ብዙ ቅዱሳን አባቶቻችንን በልዩ ልዩ ስጋዊ መከራ በማሰቃየት ለሰማዕትነት አብቀተዋቸዋል፡፡ ሰማዕታትም የሚመጣባቸውን መከራ በመታገስ እና ሁሉን ቻይ የሆነውን የአምላካቸውን ስም በመጥራት እና እስከሞት ድረስ በመታመን የድል አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡ ከሐዋርያት የተረከቧትን እወነተኛዋን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትንም ከእነሱ በኋላ ላለው ትውልድ አስተላልፈዋል፡፡ከእነሱ በኋላ የተነሱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንም ሳትበረዝ እና ሳትከለስ አሁን ላለው ትውልድ አስተላልፈዋታል፡፡ የሚገርመው ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት የተነሱ ሆድ አደሮች፤ አይነ ስጋቸው ብቻ የተከፈተላቸው አይነ ልቡናቸው ግን የታወረባቸው፤ ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ ከገለጻቸው ጣዖታት የማይሻሉ ማለትም ሕይዎት ያላቸው ተንቀሳቃሽ ጣዖታት የሚያሰሙት የትታደስ ጩኸት ነው፡፡ በጣም የሚገርም እና የሚደንቅ ነገር ነው፡፡ በእውኑ እነዚህ ሰዎች የእምነት አርበኛ ከነበሩት፣ ሌሊት ከቀን ለጸሎት እና ለስግደት ይተጉ ከነበሩት፣ ሀይማኖታችንን አናስለውጥም፣አንክድም ብለው እሰከመጨረሻው ድረስ በመታገስ መራራ ሞትን ከቀመሱት ቅዱሳን አባቶቻችን ይበልጣሉን? ይህንን ጥያቄ ሁላችን በህሊናችን ልንጠይቅ ያስፈልጋል፡፡ የቤተክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች ሆይ እነዚህ ሰዎች እራሳቸው ጠፍተው ሰውን ለማጥፋት የተነሱ የዲያብሎስ መልእክተኞች ናቸውና ማንነታቸውን በመረዳት ከቤታችን ልናስወጣቸው ያስፈልጋል፡፡ በምን እናውቃቸዋለን ብንል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መመሪያ ሰጥቶናል ይኸውም “ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ” የሚል ነው፡፡ ማንም ሰው ጌታችን በደሙ ከመሰረታት እና ለሐዋርያት ከሰጣት ከአንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት እና ስርዓት ውጭ እንግዳ ትምህርት እና የእምነት ዶግማ እንዲሁም ቀኖና እና ስርዓት የሚያመጣ ሁሉ እርሱ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ወገን አይደለም፡፡እነዚህ ሰዎች ምንም ሳይማሩ ታሪክ አዋቂ በመምሰል እና አዲሱን ትውልድ ለማወናበድ እንዲሁም በግብጽ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የአባይ ጉዳይ እንደ ክፍተት በመጠቀም አሁን በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ያለውን አውነተኛ ዶግማ እና ስርዓት የግብጽ ሰዎች ኢትዮጵያን ለመበቀል እና ኋላቀር ለማድረግ ያመጡት ስርዓት ነው በማለት የትታደስ ጩኸት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ እውነታው ግን እነሱ እንደሚሉት አይደለም፡፡ ስለዚህ ክፍተት የሚመስሉ ነገሮችን እንደ መነሻ ሀሳብ በማንሳት እውነታውን ግን ጥላሸት በመቀባት በአባቶቻችን ዘመን ታይቶ የማይታወቅ አስተምህሮ ቀስ በቀስ ወደቤተክርስቲያን ውስጥ በማስገባት፤ እያወቁም ይሁን ሣያውቁ የሚከተሏቸውን የውኃንን ለዲያብሎስ እራት ለማድረግ የሚተጉ፣ ዐይን እያላቸው የማያዩ እና የማያስተውሉ ተሃድሶወችን ይህንን ስውር ሴራ እንደያዙ አውቀን ልንቃወማቸው ያስፈልጋል፡፡ አምላክ ቅዱሳን ቤተክርስትያናችንን ከውጭ ወራሪ ከውስጥ ጠላት ይጠብቅልን እኛንም በቤቱ ያጽናን አሜን!!!
ክክክክ የሚገርም ጉድ
በዚህ ክፍል ደግሞ በመድረክ ላይ ሆኖ ከተናገራቸው ቃላት ወስጥ የተወሰኑትን እንይ
1•"ልጸልይላችሁ" ይህንን ቃል ስሰማ በጣም ገረመኝ ምክንያቱም ትናንት ከትናንት ወዲያ በየቦታው አማላጅ አያስፈልግም፣ ድንግል ማርያም አታማልድም፣ ቅዱሳን አያማልዱም እያሉ ሲከራከሩ የነበሩ ሰዎች ዛሬ ዛሬ እንዲህ አይነት ቃላትን ሲቀበሉ ስላየሁ ነው። እዚህ ላይ ማየት እና ማስተዋል ያለብን ነገር
* በእውኑ ይህ ሰው ከቅድስት ድንግል ማርያም ይበልጣልን? የሚለውን ጥያቄ ነው። ይህ ሰው እንኳን ከቅድስት ድንግል ማርያም ሊበልጥ እና እኩል ሊሆን እግሯ የረገጠውን ትቢያ እንኳ መሆን አይችልም። ድንግል ማርያም ማለት አደፍ ጉድፍ የሌለባት ንጽሕት ዘር ናት። ነቢያት ትንቢት የተናገሩላት፣ ምሳሌ የመሰሉላት፣ አዳም ከወደቀበት የኃጢአት ጉድጓድ የወጣባት፣ ሔዋን ከታሰረችበት የኃጢአት ማሰሪያ የተፈታችባት፣ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር የነበረች በኋላም የተስፋው ጊዜ ሲደርስ አምላክን በማህጸኗ ለመሸከም በቅታ የተገኘች በአጠቃላይ ለፍጥረታት ሁሉ የድህነት ምክናያት የሆነች ድንቅ ልዩ ፍጥረት ናት። ስለዚህ አባቶቻችን ስለ ድንግል ማርያም የተነገረውን እና የተደረገውን ነገር ሁሉ ጠንቅቀን መናገር አይቻለንም እና ዝም እንበል እንዳሉ ሁሉ እኛም ከእነሱ አንበልጥም እና አፈጣጠሯን እና ልዩ ጸጋዋን እያደነቅን በበረከቷ በአማላጅነቷ በእናትነቷ ጸጋ መጠቀም ይሻለናል። ስለዚህ ድንግል ማርያምን አታማልድም ብሎ በድፍረት የተሳደበ አፍ ዛሬ እኔ አማልዳለሁ(ለሌሎች እጸልያለሁ) ሲል መስማት በጣም የሚገርም ነገር ነው። የሚናገረው ሰውም ጤነኛ አዕምሮ የለውም። የሱን ሀሳብም በእልልታ እና አሜን በማለት የተቀበሉ ሰዎች በእውነት መነሻ እና መድረሻቸውን ያላወቁ፣ ሁለት የማይጣጣም ነገርን በአንድ ይዘው ለመጓዝ የሚሞክሩ፣ ለጊዜው በስጋዊ ፈቃዳቸው ደስተኛ ሆነው ማለትም አንዴ ጸድቀናል በሚል ተልካሻ ምክናያት እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ ኃጢአትን ለመስራት የሚፈልጉ ሞኞች ናቸው። እዚህ ላይ ሌላው ማስተዋል ያለብን ነገር ቅዱሳን ቅድስናቸውን ያገኙት ስለአምላካቸው በአላውያን ነገስታት እና በሀሳውያን ነቢያት ፊት መስክረው የደረሰባቸውን መከራ እስከ ሞት ድረስ በመታገስ እና በጸኑ መከራ ወስጥ በማለፍ ነው። ቅድስናቸውንም የመሰከረላቸው መከራውን እንዲታገሱ ጽናት እና ትዕግስት እንዲሁም ማስተዋልን የሰጣቸው ሁሉን ቻይ የሆነው አምላካቸው ነው። ስለዚህ መናፍቃን የቅዱሳንን ቅድስና ተቀበሉም አልተቀበሉም ለራሳቸው ይቀርባቸዋል እንጅ ከቅዱሳን የሚቀንሱባቸው አንዳች ነገር የለም። ምክናያቱም እግዚአብሔር ያከበረውን ማንም ዝቅ ማድረግ አይችልም እና ነው። በአጠቃላይ እንዲህ አይነት ነገሮችን) የምናመዛዝንበት ህሊና ስለተሰጠን መጥፎውን ከጥሩው፣ ጨለማውን ከብርሐን ለይተን እራሳችንን አውቀን ጥሩውን መንገድ ልንከተል ያስፈልጋል። ድንግል ማርያም በምልጃዋ ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ትሰውረን አሜን
ክክክክ የሚገርም ጉድ
እሱም ከፍተኛ ሞራል ስለተሰማው እራሱን ከቅዱሳን ሐዋርያት ጋር
በማስተካከል ልሳን ተገለጸልኝ በሚል መንፈስ እንኳን ለሚሰሙት ለራሱ እንኳ ትርጉሙን በማያውቀው ቋንቋ በመሰለ ነገር
ይንተባተብ ጀመር። ልብ ብሎ በእውነተኛ ህሊና ለሚመለከተው እና ለሚመረምረው ሁሉ ነገሩ ርኩስ መንፈስ በሰዎች ላይ
ሲሰለጥን የሚመጣ ባዶ መንተባተብ እንጅ የመንፈስ ቅዱስ አይደለም። ምክንያቱም ከቅዱሳን ሐዋርያት እና ከቀደሙት
ቅዱሳን አባቶቻችን እንደሰማነው እና እንደምንረዳው በመንፈስ የተገለጠላቸው ልሳን ተናጋሪዎችም ጠንቅቀው የሚያውቁት
ትምህርታቸውን የሚከታተሉት ሰዎችም ራሳቸው በሚያውቁት እና በሚግባቡበት ቋንቋ እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል።
የሐዋርያት ስራ 2:6—12 ስለዚህ በዚህ ሰውየ ላይ መንፈስ ቅዱስ አድሮበታል ብለው የሚያምኑ ሰዎች
በእውነት መጽሐፍ ቅዱስን ተሸክመው የሚዞሩ እና ከላይ ከላይ ለእነሱ ብቻ የሚመቹ ጥቅሶችን የሚያነበንቡ ምስጢሩ
ግን ያልገባቸው ለሰው ልጆች ሁሉ ብርሐን የሆነችውን አንዲቱን ተዋህዶ እምነትን እንዳይከተሉ ዘመናዊ በሆነ ጠንቋይ
ቅሰጣ አይነ ልቡናቸው የታወሩ ሰዎች መሆናቸውን ሳይ በጣም ተገረምኩም አዘንኩም። ስለዚህም ነገር ሌሎችም የውሃን
የሆኑ ሰዎች የሚያዩት እና የሚሰሙት ነገር እውነት መስሏቸው እውነተኛዋን መንገድ ትተው ወደ ጨለማ እንዳይገቡ
ለማሳሰብ ስል ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ተገደድኩ። አምላከ ቅዱሳን ከገቡበት የጨለማ ሕይዎት ወደ ብርሀን ይመልሳቸው
እኛንም ከእንደዚህ አይነት መጥፎ ሕይዎት ይጠብቀን አሜን!!! ሌላ ብዙ የገረመኝ ነገር ስላለ በክፍል ሦስት ጠብቁኝ
ይቀጥላል
"ክክክክ የሚያስቅ እና የሚገርም ነገር"
በዚህ ሳምንት የገጠመኝን ልንገራችሁ በአቢይ ጾም ይህን ያህል ሳቅ ምንድን ነው ማለታችሁ አይቀርም ነገር ግን እኔ ያየሁትን ነገር ጊዜ ገጥሟችሁ እናንተም ብታዩት ከዚህ የበለጠ ትገረሙ እና ትስቁ ነበር። ነገሩ ምንድን ነው ካላችሁ ነገሩ እንዲህ ነው እና አንቡት።
አንድ ቀን ከስራ እንደተመለስኩ ከደሳሳዋ ዶርሜ ቁጭ ብየ ሳለሁ በአጋጣሚ ቴሌቭዥን መክፈት ከዚያም ሪሞቱን እየነካካሁ ከላይ ወደ ታች ያሉ የቴሌቪዥን ቻናሎችን በመፈለግ ላይ ሳለሁ በአጋጣሚ አይኔ ላይ የሆነ ነገር ድቅን አለ። እኔም ምንድን ነው ብየ ስለተገረምኩ የሚተላለፈውን ነገር ማየት ጀመርኩ። ከዚያም "ስንት ሰው በዚህ እዚህ ግባ በማይባል ተረት ውስጥ ተደብቆ ይሆን?" ብየ እራሴን ጠየቅኩ። ሰዎች ያሉ የሆነ አዳራሽ ውስጥ ነው አንድ ሱፍ የለበሰ ሰውየ ከመድረክ ላይ ማይክ ይዞ እንደ አገሬ ፎካሪ ከወዲያ ወዲህ ይንጎራደዳል። እኔም ምን ሊያደርግ ነው? ብየ ስመለከት ከፍ ባለ ድምጽ እንዲህ ብሎ ጮኸ።
"አንች ከኋላ የቆምሽ ሴት" አለ። የሚገርመው ነገር ከኋላ የቆሙት ሴቶች ብዙ ነበሩ የትኛዋን ሴት እንደሆነ ግን ግልጽ አይደለም። ሰውየው የተናገረውን ነገር ስሰማ እና ስለ ጠንቋይ ሰዎች ሲያወሩ የሰማሁት ነገር ስለተመሳሰለበኝ እንዲህ ብየ አሰብኩ "በቃ ጠንቋይ እንዲህ በይፋ በመድረክ ላይ ማይክ ይዞ የማይሆን ተስፋ በመስጠት የዉሃንን ወደ ጨለማ ያመላልሳል።" ይህን እያሰብኩ እያለ ሰውየው ቀጠለ በድጋሜ "አንችን እኮ ነው" አለ የቆሙት ሴቶች ለራሳቸው ሳይገርማቸው አልቀረም። ምክንያቱም እርስ በራሳቸው ተያዩ እና ከመካከላቸው አንዷ "እኔን ነው?" አለች እሱም "አዎ አንችን ነው" አላት ከዚያም በመቀጠል "ከሰዓት ነው የመጣሽ አይደል?" አላት እሷም አዎ አለች። ከዚያም "የአባትሽ ስም ጌታቸው ነው የሚባል አይደል?" አላት እሷም "አዎ" አለች ከዚያም "የሆነ ነገር ቸግሮሻል አይደል? ስለምንድን ነው እንድጸልይልሽ የምትፈልጊ?" አላት እሷም ጥያቄው እውነት ስለመሰላት እንዲህ ብላ መለሰች "ልጆቸ በእዳ ስለተያዙ እዳቸው እንዲከፈል ነው" አለች የሚገርመው ነገር እሱ እና እሷ ቃለ ምልልስ በሚያደርጉበት ጊዜ ከመሀል "አሜን" የሚል ድምጽ ይሰማ ነበር። ይህንን ስሰማ ሰውየው ሰባኪ ሳይሆን ጠንቋይ መሆኑን በደንብ አረጋገጥኩ ምክንያቱም ከዚህ በፊት ጠንቋይ ቤት የሄዱ ሰዎች ጠንቋዩ በሚናገርበት ወቅት ታዳሚዎች "አሜን በእርስዎ መጀን" እያሉ የድለላ እና የሽወዳ ስራውን እንደሚያጅቡለት ሰምቻለሁ። ከዚያ በመቀጠለም ሰውየው እንዲህ በማለት ይፎክር ጀመር "በእየሱስ ስም የልጆችሽ እዳ ይከፈላል" ታዳሚዎችም አሜን በማለት ስብሰባውን አደመቁት። ይቆየን ይቀጥላል
Subscribe to:
Posts (Atom)



