Thursday, June 23, 2016

ማስረጃ ወይስ ሰውን መሸወጃ (ክፍል ሦስት)



በክፍል ሁለት መዝሙር 2÷7 ያለውን አይተናል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ ሮሜ 1÷2-4 ያለውን እናለን፡፡ እዚህ ላይም እንድትረዱት የምፈልገው ነገር እነ አዲሱ እና መሰሎቻቸው አባቲቻችን በመንፈስ ቅዱስ የተረጎሙትን እነሱ ግን  ምንም ሳይገባቸው እና ምስጢሩን ሳይረዱ አዋቂ ለመባል ብቻ በራሳቸው መንገድ እየተረጎሙ እንደ ማስረጃ ብለው የሚያቀርቡት መሆኑን እንድትረዱ እና እውነታውን እንድታውቁት  ነው፡፡ ለዚያም ያመቸኝ ዘንድ ነው አንድምታው ላይ ያለውን ምንም ሳልጨምር ሳልቀንስ የምጽፍላችሁ፡፡
በመጀመሪያ አዲሱ  እና ተከታዮቹ የተረጎሙትን አቀርብላችሁና ቀጥሎ ደግሞ  የቤተክርስቲያን ሊቃውንት አባቶቻችን ተርጉመው ካስቀመጡት አንድምታ ትርጓሜ ላይ ያለውን ቃል ሙሉ በሙሉ አቀርብላችኋለሁ፡፡
መልካም ንባብ
ሮሜ 1÷2-4 ”በእንተ ወልዱ ዘተወልደ ወመጽአ እም ዘርአ ዳዊት በስጋ ሰብእ ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ ወበመንፈሱ ቅዱስ“ አቶ አዲሱ እና ተከታዮቹ ሲተረጉሙት እንዲህ ይሉታል፡፡
”በእንተ ወልዱ ዘተወልደ“ ማለቱ  እምቅድመ ዓለም በመለኮቱ  ከአብ የተወለደውን ልደት ሲናገር ነው፡፡
“ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ ወበመንፈሱ“ ማለቱ መለኮት ሰው ቢሆን በማኅጸነ እግዝእትነ ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከአብ የተወለደውን ልደት ሲናገር ነው፡፡
“ወመጽአ እም ዘርአ ዳዊት በስጋ ሰብእ” ማለቱ ደግሞ ከእግዝእትነ ማርያም በስጋ መወለዱን ሲናገር ነው ብሎ ተርጉሞታል፡፡
ከዚህ ቀጥለን ደግሞ አንድምታ መጽሐፉ ላየረ ያለውን ትርጉም እንመልከት
መጽሐፉ ሲጀምር እንዲህ ይላል፡- ”ዘአቅደመ ነጊረ በአፈ ነቢያቲሁ ቅዱሳት በእንተ ወልዱ ዘተወልደ” ትርጉሙም፡- አካል ዘእም አካል፣ ባሕርይ ዘእም ባሕርይ የተወለደ የልጁን ነገር ፤ ስለ ተወለደ ስለ ልጁ፤ በዳዊት፡- ”ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ“መዝ 2÷7፤ በነገስት፡- “አነ እከውኖ አባሁ ወውእቱ ይከውነኒ ወልድየ” 2ኛ ነገ 7÷14፤ በሰሎሞን፡- ”እምቅድመ አድባር ወአውግር ወለደኒ“ ምሳሌ 8÷25፤ በነቢያት በመጻሕፍት  ያናገረ የአብን ነገር ከማስተምር ከእኔ ከጳውሎስ የተገኘች ክታብ (መልእክት)
ሐተታ ፡- መጻሕፍት፣ ነቢያት የሚሏቸው ልዩ ናቸውን ቢሉ ፡-
ነቢያት ያላቸው ሳሉ የተናገሩት፡፡ መጻሕፍት የሚላቸው ከሞቱ በኋላ የተጻፉት ናቸው፡፡ ይህማ ሳሉ የተናገሩት ከሞቱ በኋላ ቢጻፍ ልዩ ነውን ብሎ ነቢያት የሚላቸው አድሮ ያናገራቸው፡፡ መጻሕፍት የሚላቸው በዘፈቀደ ታይቶ ያጻፋቸው ናቸው፡፡ ቅዱሳት ንጹሐት ክቡራት ሲል ነው፡፡ ርኩሳት መጻሕፍተ ጥንቆላ አሉና ከዚያ ሲለይ ንጹሐት አለ፡፡
ምኑናት መጻሕፍተ ደብዳቤ አሉና ከዚያ ሲለይ ክቡራት አለ፡፡
“ወመጽአ እም ዘርዐ ዳዊት በስጋ ሰብእ ” ትርጉሙም፡- በስጋ ከዘርዐ ዳዊት ስለተወለደ ስለ ልጁ፤ የተወለደ የልጁን ነገር በኢሳይያስ ” ትወጽእ በትር እምስርዎ እሴይ  ወየዐርግ  ጽጌ እምጉንዱ””ወይቀውም ሥርዎ እሴይ ወዘተወልደ እምኔሁ ይከውን ንጉሠ ለአሕዛብ“ ኢሳ 11÷1 እና 10፤ በዳዊት “ እስመ እምፍሬ ከርስከ አነብር ዲበ መንበርከ ” መዝ 132÷1 ብሎ በነቢያት በመጻሕፍት ያናገረ የአብን ህግ ከማስተምር ከእኔ ከጳውሎስ
ሐተታ፡- ሥጋ እንስሳ አለና ከዚያ ሲለይ ስጋ ሰብእ አለ፡፡ ምነው ዘርዐ ዳዊት ያለው አይበቃምን ቢሉ ነፍስን እንደነሳ ለማጠየቅ ፤ ያውስ ቢሆን ”ዘርዐ አብርሐም አልዐለ“ እንዲል(ዮሐንስ አፈወርቅ) ዘርዐ ዳዊት ያለው አይበቃምን ቢሉ  በከዊን ሲል ነው፡፡ ”ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር በኃይሉ ወበመንፈሱ ቅዱስ” ትርጉሙም ፡- ”ዘተወልደ ወዘአርአየ “ ብሎ ለወልድ ይቀጽላል፡፡ ኃይሉ ሕይዎቱ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስ ከዘርዐ ዳዊት በመወለዱ ወልደ እግዚአብሔር እንደሆነ ስላሳየ ፣ ስለ ልጁ ያሳየ፣ የልጁን ሕግ ወንጌልን ከማስተምር ከእኔ ከጳውሎስ
ሐተታ፡- አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከእመቤታችን ያለ አባት መወለዱ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት መወለዱን ያስረዳልና፡፡ “ልደት ቀዳማዊ ተዐውቀ በደኃራዊ ልደት”  እንዲል (ሃይማኖተ አበው ሱኑት)
አንድም፡ በኃይሉ፡- በኅቱም ድንግልና ተጸንሶ በኅቱም ድንግልና በመወለዱ ፡፡ ወበመንፈሱ ቅዱስ ፡- መንፈስ ቅዱስን በዮርዳኖስ በርግብ አምሳል በእራሱ ላይ በማኖሩ ፡፡”አሜሃ ስምዐ ኮነ መንፈስ በዮርዳኖስ ከመ ወልድ ዘበአማን ወአምላ ዘበአማን“ እንዲል ቄርሎስ
አንድም፡ በኃይሉ፡- 3 አመት 3 ወር ባደረገው ተአምራት፡፡
ወበመንፈሱ ቅዱስ፡- መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን በመስደዱ ፡፡
አንድም፡ “ዘአቅደመ ወዘአርአየ” ብሎ ለአብ ይቀጽላል፡፡ ”በኃይሉ ከመ ወልደ እግዚአብሔር አርአየ በመንፈስ ቅዱስ“ ሲተረጎም፡ በባሕርዩ ወልደ እግዚአብሔር እንደሆነ መንፈስ ቅዱስን በእራሱ ላይ በማኖር ያሳየ የልጁን ነገር፡፡
 አንድም ፡ “በመንፈስ ቅዱስ ከመ ወልደ እግዚአብሔር አርአየ በኃይሉ” በግብረ መንፈስ ቅዱስ በመወለዱ ወልደ እግዚአብሔር እንደሆነ በግብሩ፣ በነገሩ አሳየ አለ፡፡  በነገሩ፡- ”ዝንቱ ውእቱ ወልድየ“ ብሎ፡፡ በግብሩ፡- መንፈስ ቅዱስን በርግብ አምሳል በእራሱ ላይ በማኖሩ ያሳይ የልጁን ነገር በኢሳይያስ “ቁልዔየ ፍቁርየ ዘሰምረቶ ነፍስየ ወአነብር መንፈስየ ላዕሌሁ ”ኢሳ 11፡2
ከዚህ በላይ ቤተክርስቲያን ከምትጠቀምበት የአንድምታ ትርጓሜ መጽሐፍ ያለውን ቃል ሙሉ ትርጉሙን  እንዳየነው

No comments:

Post a Comment