Thursday, June 23, 2016

ማስረጃ ወይስ ሰውን መሸወጃ ክፍል አራት



“ወአርአየ ከመ ወልደ እግዚአብሔር ውእቱ በኃይሉ ወበመንፈሱ“ የሚለው ቃል ”መለኮት ሰው ቢሆን በማኅጸነ እግዝእትነ ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከአብ የተወለደውን ልደት ሲናገር ነው“፡፡ የሚል ትርጉም የለውም፡፡
ስለዚህ አዲሱ እና መሰሎቹ የቅባት እምነት ተከታዮች በሚመቻቸው መልኩ መተርጎምና ሰዎችን ማወናበድ ጀምረዋል ማለት ነው፡፡ እንዲህ ከሆነ ደግሞ ጌታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ቃል ማለትም “ይቀልል ኅልፈተ ሰማይ ወምድር እምትደቅ አሃቲ ቃል እም ኦሪት ወእም ነቢያት” ትርጉሙም “ከኦሪት እና ከነቢያት አንዲት ቃል ከምትወድቅ የሰማይ እና የምድር ማለፍ ይቀላል” የሚለው ቃል ተሸሯል ማለት ነው፡፡ አምላካችን ይህንን ቃል የተናገረው እንመራበትም ዘንድ በመጻሕፍት በቅዱሳን ላይ አድሮ ያጻፈው ህጉን አክብረን እንድንጠቀም ነው፡፡ በክፍል አንድ ላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት የቅብዓት እምነት ተከታዮች  ”መለኮት ሰው ቢሆን በማኅጸነ እግዝእትነ ማርያም በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከአብ ተወለደየምትለዋን የክህደት ፍልስፍና  እና የጨለማመንገድ እንደ እውነታ አስመስሎ በማቅረብ እውነታውን ያልተረዱ የዉኃንን ለማደናገር ነው ማለት ነው፡፡ በአጠቃላይ በዚህ አይነት በተሳሳተ መንገድ እየተረጎሙ ለሌሎች መሰናክል ከመሆን እውነታውን ተረድቶ ወደ እውነተኛዋ መንገድ መመለስ ጥሩ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ እንደ ሳጥናኤል አሻፈረኝ ቢሉ መጨሻው ውርደት እና ሞት ነው፡፡ ስለዚህ በማስተዋል ቅዱሳን አባቶቻችን ያስተማሯትን ከዚያም አልፎ ሕይዎታቸውን ለስጋ ሞት አሳልፎ እስከ መስጠት ድረስ የታመኑላትን እምነት አጽንተን መከተል ያስፈልጋል፡፡ አምላከ ቅዱሳን በክህደት መንገድ ለተጠመዱት ማስተዋሉን ያድልልን!!!

No comments:

Post a Comment