ስላሴ ሶስት ከሚሆኑባቸው ነገሮች አንዱ የከዊን ሶስትነት ነው፡፡ ይህም ከዊነ ልብ፣ ከዊነ ቃል እና ከዊነ እስትንፋስ ናቸው፡፡ ምንም እንኳ ስላሴ በከዊን ሶሰት ቢሆኑም በህልውና በመገናዘብ ደግሞ እንድ ይሆናሉ፡፡ ይህም እንዴት ነው ብትሉ እንደሚከተለው ነው፡፡ ይህም ማለት በአብ ልብነት ወልድም መንፍስ ቅዱስም ያስቡበታል፡፡ በወልድ ቃልነት አብም መንፈስ ቅዱስም ይናገሩበታል፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት(ሕይወትነት) አብም ወልድም ለዘለዓለም ሕያዋን ሆነው ይኖሩበታል፡፡ ይህ በስላሴ በህልውና የመገናዘብ ሁኔታ ቀድሞም አልተለያየም፡፡ አሁንም አልተለያየም፡፡ ወደፊትም ቢሆን አይለያይም፡፡ ይህና ያመጣሁበት ዋናው ምክንያት ሰው ምስጢረ ተዋሕዶን ለመረዳት መጀመሪያ ይህንን ረቂቅ ምስጢር መረዳት ስለሚገባ ነው፡፡ ትንሽ ስለረዘመ ነው ምሳሌው በክፍል አራት ይቀጥላል፡፡
Saturday, May 6, 2017
“እርሱ በተዋሕዶ ሰው የሆነ አምላክ ነው”
ስላሴ ሶስት ከሚሆኑባቸው ነገሮች አንዱ የከዊን ሶስትነት ነው፡፡ ይህም ከዊነ ልብ፣ ከዊነ ቃል እና ከዊነ እስትንፋስ ናቸው፡፡ ምንም እንኳ ስላሴ በከዊን ሶሰት ቢሆኑም በህልውና በመገናዘብ ደግሞ እንድ ይሆናሉ፡፡ ይህም እንዴት ነው ብትሉ እንደሚከተለው ነው፡፡ ይህም ማለት በአብ ልብነት ወልድም መንፍስ ቅዱስም ያስቡበታል፡፡ በወልድ ቃልነት አብም መንፈስ ቅዱስም ይናገሩበታል፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት(ሕይወትነት) አብም ወልድም ለዘለዓለም ሕያዋን ሆነው ይኖሩበታል፡፡ ይህ በስላሴ በህልውና የመገናዘብ ሁኔታ ቀድሞም አልተለያየም፡፡ አሁንም አልተለያየም፡፡ ወደፊትም ቢሆን አይለያይም፡፡ ይህና ያመጣሁበት ዋናው ምክንያት ሰው ምስጢረ ተዋሕዶን ለመረዳት መጀመሪያ ይህንን ረቂቅ ምስጢር መረዳት ስለሚገባ ነው፡፡ ትንሽ ስለረዘመ ነው ምሳሌው በክፍል አራት ይቀጥላል፡፡
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment